የሀገር ውስጥ ዜና

ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ተወካዮች ጋር ተወያዩ

By Amele Demsew

August 31, 2023

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በከተማና መሰረት ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ የተመራ ልዑካን ቡድን ከፈረንሳይ የልማት ድርጅት ተወካዮች ጋር ተወያይቷል፡፡

በውይይታቸውም÷ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ የሆኑ ተጨማሪ የትብብር ፕሮጀክቶችን በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

በተጨማሪም÷ እስካሁን በድርጅቱ የተከናወኑ የትብብር ሥራዎችም የሚበረታቱ መሆናቸው በውይይቱ መነሳቱን በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡