Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከ22 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 13 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከ22 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉሙሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የተያዙት እቃዎች 112 ነጥብ 8 ኪሎ ግራም የሚመዝኑ የብር ጌጣጌጥ፣ መድሃኒት፣ ሞባይል መለዋወጫ እና የተዘጋጁ ልብሶች መሆናቸው ተገልጿል፡፡

እቃዎቹ ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡ መንገደኞች ላይ በተለይ በዝቅተኛ የሥጋት ደረጃ በሚስተናገዱ መንገደኞች እና ይዘዋቸው በሚገቡ ሻንጣዎች ላይ በተደረገ ጥብቅ የቁጥጥር ስራ ነው የተያዙት ፡፡

በኮንትሮባንድ ዝውውሩ ተሳታፊ የሆኑ ኮንትሮባንዲስቶች፣ ደላሎች እና ሌሎች አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑንም የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version