Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 12 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶች ፕሬዚዳንት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንቱ አዲስ አበባ ሲገቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “እያደገ የመጣው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በመከባበር እና ለጋራ እድገት የጋራ ራዕይ ላይ የተመሰረተ” መሆኑን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

ዘላቂ ልማትን ለማስቀጠል ትብብራችንን እንቀጥላለንም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

Exit mobile version