አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ ከኳታር ባለሙሉስልጣን አምባሳደር ሐማድ ቢን ሞሐመድ አል-ዶሳሪ ጋር ተወያዩ፡፡
በውይይታቸውም÷ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
በተጨማሪም÷ ሀገራቱ በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በጤና ነክ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!