Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምስት ሀገራት መሪዎች ስብሰባ ላይ ተሳተፉ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 17 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ከሰዓት በኋላ የአምስት ሀገራት መሪዎች ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል።

በስብሰባው ኢትዮጵያን ጨምሮ የጣሊያን፣ የጅቡቲ፣ የሶማሊያ እና የኬንያ የመሪዎች መገኘታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

ስብሰባው በሀገራቱ መካከል የተቀናጀ ትብብር እንዲኖር የጋራ በሆኑ ጉዳዮች እና ፍላጎቶች ላይ ለመምከር የተዘጋጀ ነው ተብሏል።

Exit mobile version