Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በለንደን ዳይመንድ ሊጉ ጉዳፍ ፀጋየ  አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በለንደን ዳይምንድ ሊጉ የ5 ሺህ ሜትር ወድድር  አትሌት ጉዳፍ ፀጋየ ድል ቀንቷታል፡፡

ጉዳፍ  ርቀቱን ለመጨረስ 14 ደቂቃ ከ12 ሴኮንድ የፈጀባት ሲሆን ተቀናቃኞቿን ሲፈን ሀሰን እና ብያትሪስ ቺቤትን በመቅድም ነው የ5 ሺህ ሜትር እርቀቱን በበላይነት ያጠናቀቀችው፡፡

በርቀቱ ኬንያዊቷ ብያትሪስ ቺቤት 2ተኛ እንዲሁም ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ  እና ለኔዘርላንድስ የምትሮጠው አትሌት ሲፈን ሀሰን 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል፡፡

የኦሪገኑን ድርብ ድል በቡዳፔስት ለመድገም እየተዘጋጀች  የምትገኘው ጉዳፍ ፀጋየ የዛሬው ድሏ በአለም ሻሚዮናው ተጠባቂ አትሌት እንድትሆን አስችሏታል፡፡

Exit mobile version