Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የፊታችን ሐምሌ 8 ቀን የኢትዮጵያ የፕሪሚየር ሊግ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ይከፈታል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከፊታችን ሐምሌ 8 ቀን ጀምሮ የኢትዮጵያ ወንዶች እና ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ተጫዋቾች የዝውውር መስኮት እንደሚከፈት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡

የዝውውር መስኮቱ ከሐምሌ 8 ቀን እስከ መስከረም 25 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ተገልጿል፡፡

የተጫዋቾች ዝውውር ሕጋዊነት የሚፀድቀውም÷ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ጽሕፈት ቤት ተገኝቶ በመፈራረም ብቻ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በክልል እግር ኳስ ፌደሬሽኖች እና በሌላ አካል በኩል የሚደረግ ስምምነት ተቀባይነት የለውም መባሉን   የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version