Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ፌዴሬሽን የአስተዳደር ቦርድ አጥኚ ኮሚቴ አባላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የበላይ ጠባቂ ሣኅለወርቅ ዘውዴ የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ፌዴሬሽን የአስተዳደር ቦርድ አጥኚ ኮሚቴ አባላትን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

የኮሚቴ አባላቱ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡

ከጉብኝታቸው በኋላም ከፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ የኢትዮጵያ ቀይመስቀል ማኅበር እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ መክረዋል፡፡

የተጠናከረ ትብብር እና ድጋፍ መደረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይም መወያየታቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

 

 

Exit mobile version