Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

“ፋይዘር” በኢትዮጵያ መድሐኒቶችን ያለትርፍ ማቅረብ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው “ፋይዘር” የመድሐኒት እና የክትባት አምራች ኩባንያ በኢትዮጵያ ጥራት ያላቸው መድሐኒቶችን ያለትርፍ ማቅረብ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ከአምባሳደር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር ኢ/ር) ጋር መከረ፡፡

በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር ኢ/ር) ከፋይዘር ዓለም አቀፍ የአዳጊ ገበያዎች ፕሬዚዳንት ኒክ ላኖዊች ጋር መወያየታቸውን በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል፡፡

በውይይቱም ÷ የኩባንያው ሥራ አሥፈፃሚዎች ቡድን “ሥምምነት ለጤናማ ዓለም” በሚል ዓላማ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው 45 አዳጊ ሀገራት መድሐኒቶችን እና ክትባቶችን ያለትርፍ ለማቅረብ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ለመምከር ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣ ተገልጿል፡፡

አምባሳደር ስለሺ(ዶ/ር ኢ/ር) ÷ ትብብሩ የአዳጊ ሀገራቱ ዜጎች ከፍተኛ ጥራት እና ውጤታማ መድሐኒቶችን እንዲያገኙ ያግዛል ብለዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version