አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስልክ ተወያዩ።
ውይይቱን አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በትዊተር ገፃቸው፥ “ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር የኢትዮ-አሜሪካን ግንኙነት የበለጠ በማጠናከር ዙሪያ አበረታች የስልክ ውይይት አድርገናል” ብለዋል።
“የኮቪድ መከላከል እና ቅነሳ ጥረቶች እንዲሁም በበረሃ አንበጣ ቁጥጥር ላይ የሚደረገውን ድጋፍ ለማድነቅ እወዳለሁ” ሲሉም ገልፀዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው በትዊተር ገፃቸው ፥ “ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያይተናል” ብለዋል።
“ኢትዮጵያ የህክምና የመተንፈሻ መርጃ (ቬንቲሌተሮች) ያስፈልጓታል” ያሉት ፕሬዚዳንት ትራምፕ፥ “አሜሪካም ድጋፍ ለማድረግ በጥሩ አቋም ላይ ትገኛለች፤ ይህንንም እናደርጋለን” ብለዋል።
Encouraging phone call with @realDonaldTrump reconfirming continued US-Ethiopia relations. Appreciate the commitment of support to #COVID19 prevention and mitigation efforts as well as on desert locust control.
— Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 (@AbiyAhmedAli) April 25, 2020
Just spoke to Prime Minister Abiy Ahmed Ali of Ethiopia. His Country needs Ventilators, and the U.S. is in good position to help him. We will!
— Donald J. Trump (@realDonaldTrump) April 25, 2020
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።