Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በምሥራቅ አፍሪካ ተጎጂዎችን ለመደገፍ የሚውል 2 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር መገኘቱ ተነገረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በምሥራቅ አፍሪካ የሚያደርገውን እርዳታ ለመደገፍ የሚውል 2 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር አገኘ።

የተገኘው ገንዘብ ድርጅቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ በኬንያ እና ሶማሊያ ለሚገኙ ወደ 32 ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎች ድጋፍ ለማድረግ የሚውል መሆኑ ታውቋል።

ድጋፉ የተመድ አጋር ከሆኑ ማኅበረሰቦች ፣ ሰብዓዊ ድርጅቶች ፣ ባለሥልጣናት እና ለጋሾች መገኘቱን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ ድጋፍ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) መረጃ ያመላክታል፡፡

ዛሬ ቃል የተገባውን የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት የተቻለው በኒውዮርክ በተዘጋጀ ከፍተኛ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ላይ ሲሆን ተመድ በምስራቅ አፍሪካ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ አደጋዎች ሳቢያ ችግር ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመርዳት 7 ቢሊየን ዶላር እንደሚያስፈልገው ገልጾ ነበር፡፡

መርሐ-ግብሩን ተመድ ፣ ጣሊያን፣ ኳታር ፣ እንግሊዝ እና አሜሪካ ከኢትዮጵያ ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ መንግስታት ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል፡፡

አሜሪካ፣ የአውሮፓ ኮሚሽን፣ ብሪታንያ፣ ጀርመን እና ኔዘርላንድስ አብዛኛውን ገንዘብ ለመስጠት ቃል የገቡ ሀገራት ናቸው።

በቀጣናው ባለፉት 5 የዝናብ ወቅቶች በቂ ዝናብ ባለመዝነቡ በተከሰተው ድርቅ፣ በግጭት ለተጎዱ እንዲሁም የሀገራቱ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ የተረጋጋ ባለመሆኑ ድጋፉ ማስፈለጉም ነው የተገለጸው፡፡

የተገኘው ድጋፍ ተጎጂዎችን በጊዜያዊነት ለመደገፍ እንጂ ችግሩን በዘላቂነት የሚፈታ እንዳልሆነ ተጠቁሟል፡፡

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version