የሀገር ውስጥ ዜና

ተቋማት ለገበታ ለትውልድ የሚያደርጉት ድጋፍ ተጠናክሮ ቀጥሏል

By Alemayehu Geremew

May 23, 2023

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ተቋማት ለገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የሚያደርጉት የገንዘብ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በ15ኛው ዙር የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት ድጋፍ ያደረጉ ተቋማትና ድርጅቶችን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህ መሰረትም አቢሲኒያ ባንክ 161 ሚሊየን 700 ሺህ ብር እና ብሔራዊ የአልኮልና አረቄ ፋብሪካ 6 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት 5 ሚሊየን እና በኢትዮጵያ የሁዋዌ ቴክኖሎጂ ኩባንያ 5 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽኅፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡