Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ሙስጠፌ መሐመድ በቶጎ ውጫሌ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ በቶጎ ውጫሌ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
 
በጉብኝት መርሐ-ግብሩ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
 
በዚህም በከተማዋ የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ፣ የከተማውን የውሃ አቅርቦት ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራትንና የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
 
አቶ ሙሰጠፌ ከጉብኝታቸው በኋላ በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር መምከራቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
Exit mobile version