Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ በአመታዊው የኢንቨስትመንት ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በአቡዳቢ እየተካሄደ በሚገኘው አመታዊ የኢንቨስትመንት ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡

በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረመስቀል ጫላ የተመራ ልኡክ በአቡዳቢ እየተካሄደ በሚገኘው 12ኛው አመታዊ የኢንቨስትመንት ጉባዔ ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ በአለማቀፍ የኢንቨስትመንት ጉባዔ ላይ መሳተፍ በዘርፉ እያሳየች ላለው እድገት በርካታ እድልን የሚከፍት ከመሆኑ ባሻገር የልምድ ልውውጦችን በማድረግ የንግድ  መዳረሻዎችን እንድታሰፋ የሚያግዝ ነው ተብሏል።

Exit mobile version