Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከንቲባ አዳነች ለ82ኛው የዐርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለ82ኛው የኢትዮጵያ ዐርበኞች ድል መታሰቢያ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከንቲባዋ በመልዕክታቸው÷የአሁኑ ትውልድ ነጻነቷ የተከበረ ሉዓላዊት ኢትዮጵያ ባለቤት እንዲሆን አባት እና እናት አርበኞች ታላቅ ተጋድሎ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሲዘከር የሚኖር ታልቅ ድል ነው ያሉት ክንቲባዋ÷ ቀጣዩ ትውልድም የአባቶቹን ፈለግ በመከተል የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version