አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ19) በኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን የከፋ ጫና ለመከላከል አስፈላጊ እርምጃዎች መውሰድ እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው እንዳስታወቁት፥ የሠራተኞችን የሥራ ዋስትናን ማስጠበቅ፣ ዘላቂ በሆነ መልኩ ገቢ እንዳይቋረጥ ማድረግ፣ እጅግ ተጋላጭ የሆኑትን የማኅበረሰብ ክፍሎች ተደራሽ የሚያደርጉ አሠራሮችን ማስፋፋት፣ የመሠረታዊ አቅርቦቶችን የግብይት ሥርዓት ማርጋት፤ እንዲሁም ለአምራች ዘርፎች ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል።