የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የታንዛኒያን የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶች ለአውሮፓ ገበያ ሊያቀርብ ነው

By Tibebu Kebede

April 19, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የታንዛኒያን የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች በሳምንት ሶስት ቀናት በረራ በማድረግ ለአውሮፓ ገበያ ሊያቀርብ ነው።

አየር መንገዱ የታንዛኒያን የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ለአውሮፓ ገበያ እንዲያቀርብ የተደረገው የሀገሪቱ የሆርቲ ካልቼር ማህበር እና የኪሊማንጃሮ ኤርፓርቶች ልማት ኩባንያ ባደረጉት ትብብር ነው።