የሀገር ውስጥ ዜና

ፀሎተ ሀሙስ በተለያዩ ኃይማኖታዊ ስነ ስርዓቶች ታስቦ ዋለ

By Tibebu Kebede

April 16, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 8፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፀሎተ ሀሙስ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በዛሬው እለት በተለያዩ ስነ ስርዓቶች ታስቦ ውሏል።

የፀሎተ ሀሙስ በዓል በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርሰቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የኢየሱስ ክርስቶስ ትህትና በተለያዩ ስነ ስርዓቶች ነው የተከበረው።