የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ ከቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይፕ ኤርዶጋን ጋር በስልክ ተወያዩ

By Tibebu Kebede

April 14, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይፕ ኤርዶጋን ጋር በስልክ ተወያዩ።

ውይይቱን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው እንዳስታወቁት፥ “የቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይፕ ኤርዶጋን ኢትዮጵያ የኮቪድ19ን ፈተናዎች እንድትቋቋም ለማገዝ ፈቃደኛ ስለ ሆኑ ደስ ብሎኛል” ብለዋል።

“ለተሳካው የስልክ ውይይት ምስጋናዬን እያቀረብሁ፤ እጅግ ተፈላጊ የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች በሚያቀርቡበት ሂደት አብሬዎት እሰራለሁ” ሲሉም ገልፀዋል።

I appreciate @RTErdogan’s interest to support #Ethiopia overcome #COVID19 challenges. Thank you for a good phone conversation and look forward to partnering in the supply of essential medical equipment.

— Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 (@AbiyAhmedAli) April 14, 2020

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!

https://t.me/fanatelevision