Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኳታሩ አል ፋይሰል ሆልዲንግስ ኩባንያ ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኳታሩ አል ፋይሰል ሆልዲንግስ ኩባንያ ሊቀመንበር ሼክ ፋይሰል ቢን ቃሲም አል ታኒ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸው የኳታሩ አል ፋይሰል ሆልዲንግ ኩባንያ በኢትዮጵያ ሊሰማራ በሚችልባቸው የንግድ አማራጮች ዙሪያ ምክክር አድርገዋል፡፡

የአል ፋይሰል ሆልዲንግ  ኩባንያ የንግድ ልዑክ ቡድን በቅርቡ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እንዲደርግም ስምምነት ላይ ተደርሷል።

የአል ፋይሰል ሆልዲንግ  ኩባንያ  በኳታር በዶሃ የሚገኝ ግዙፍ የግል የንግድ ኩባንያ ሲሆን በርካታ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version