Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

66 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከጅቡቲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 66 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከጅቡቲ በባቡር ወደ ሀገራቸው መመለሳቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።
ኤምባሲው ከዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት እና የጅቡቲ መንግስት ጋር በመተባበር ነው ስደተኞች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያደረገው፡፡
ወደ ሀገራቸው ከተመለሱት 66 ስደተኞች መካከል 57ቱ ጅቡቲ የገቡት በሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች ተመርተው ወደ ዓረብ ሀገራት ለመሻገር በማሰብ መሆኑን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
Exit mobile version