Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዓለምአቀፍ የበይነ መረብ አስተዳደር ጉባዔው ጠንካራ የበይነ-መረብ መሠረተ ልማት ላይ ሊያተኩር ይገባል – ወ/ሮ ሁሪያ አሊ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጃፓን የሚካሄደው 18ኛው ዓለም አቀፍ የበይነ-መረብ አስተዳደር ጉባዔ ጠንካራ የበይነ-መረብ መሠረተ ልማት ላይ ትኩረት ማድረግ እንደሚኖርበት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ ተናገሩ።

የዓለም አቀፉ የበይነ-መረብ አስተዳደር ጉባዔ የከፍተኛ መሪዎች ውይይት በኦስትሪያ ቪየና እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የተገኙት ሚኒስትር ዴዔታዋ ፥ ያደጉ ሀገራት የበይነ-መረብ መሰረተ ልማት ችግር ባይኖርባቸውም ታዳጊ ሀገራት ገና በዚህ ፈተና ውስጥ በመሆናቸው ጉባዔው ይህንን ሃሳብ አጀንዳ ማድረግ እንደሚኖርበት አብራርተዋል።

በፆታ፣ በቋንቋ፣ በክኅሎት፣ በኢንተርኔት ተደራሽነት፣ በዋጋ ተመጣጣኝነትና በሌሎች ጉዳዮችም የዲጂታል ክፍፍል ልዩነቶች መኖራቸውንም አንስተዋል፡፡

በዚህም በ2016 ዓ.ም በጃፓን የሚካሄደው ጉባዔ እነዚህን ጉዳዮች ታሳቢ ማድረግ ይገባዋል ማለታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

17ኛው የበይነ-መረብ አስተዳደር ጉባዔን ኢትዮጵያ በተሳካ ሁኔታ አስተናግዳ 18ኛውን ጉባኤ ለጃፓን ማስረከቧ ይታወሳል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version