የሀገር ውስጥ ዜና

በፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሚመራውና በዩኔስኮ የተቋቋመው አለም አቀፍ የትምህርት ኮሚሽን አስቸኳይ ውይይት አካሄደ

By Feven Bishaw

April 10, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሚመራውና በዩኔስኮ የተቋቋመው አለም አቀፍ የትምህርት ኮሚሽን አስቸኳይ ውይይት አካሄደ።

ውይይቱ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በትምህርት ዘርፉ ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ አስቀድሞ ለመከላከል መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ ያለመ ነው።