አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካውፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በዩክሬን ኪየቭ ድንገተኛ ጉብኝት እያደረጉ ነው፡፡
ጆ ባይደን በዩክሬን ቆይታቸው ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ፕሬዚዳንት ባይደን በፖላንድ የሥራ ጉብኝት እንደሚያደርጉም ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷“ጆሴፍ ባይደን፣ ወደ ኪየቭ እንኳን በደህና መጡ!”ም ብለዋል፡፡
የእርስዎ ጉብኝት እጅግ በጣም አስፈላጊ እና ለሁሉም ዩክሬናውያን የድጋፍ ምልክት ነው” ሲሉም ነው የገለጹት፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!