Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የማደርገው ድጋፍ ይቀጥላል – ተመድ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ዋና ጸሐፊው በውይይታቸው ላይ እየተሻሻለ የመጣውን የኢትዮጵያን የሰላም ሂደት አድንቀዋል።

ድጅቱ ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል፡፡

የድርጅቱ መሥራች አባል ከሆነችው ኢትዮጵያ ጋር ያለውን የቆየ የትብብር ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንሠራለን ብለዋ ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version