አዲስ አበባ ፣ የካቲት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ከዓለም የምግብና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ዋና ዳይሬክተር ኪዩ ዶንግዩን ጋር ተወያዩ።
በውይይታቸውም ድርጅቱ ኢትዮጵያ የምግብና የሥነ-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ላደረገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ አደጋን የመቋቋም አቅሟን ለመገንባት የግብርና ልማትን በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ አጋር በመሆን ላደረገው አስተዋጽዖና ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።