Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ከፋኦ ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 10 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ከዓለም የምግብና የግብርና ድርጅት (ፋኦ) ዋና ዳይሬክተር ኪዩ ዶንግዩን ጋር ተወያዩ።

በውይይታቸውም ድርጅቱ ኢትዮጵያ የምግብና የሥነ-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ላደረገው አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበዋል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ አደጋን የመቋቋም አቅሟን ለመገንባት የግብርና ልማትን በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ አጋር በመሆን ላደረገው አስተዋጽዖና ድጋፍ ማመስገናቸውን የፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

Exit mobile version