የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ እና ቻይና ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ተስማሙ

By ዮሐንስ ደርበው

February 15, 2023

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ እና በአፍሪካ ጉዳዮች የቻይና ልዩ መልዕክተኛ ሊዩ ዩሺ በሁለትዮሽ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መከሩ፡፡

ውይይቱ የተካሔደው ከአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ጎን ለጎን ነው፡፡

የሥራ ኃላፊዎቹ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል የቆየውን የረጅም ጊዜ ወዳጅነት አንስተው መወያየታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በቀጣይም የሀገራቱን ግንኙነት በተለያዩ መስኮች ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!