Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮ ቴሌኮምን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዛወር ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጣ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 3 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት ኢትዮ ቴሌኮምን በከፊል ወደ ግሉ ዘርፍ ለማዛወር በድጋሚ ዓለም አቀፍ ጨረታ አወጣ።

አሁን የወጣው ጨረታ የኢትዮ ቴሌኮምን 45 በመቶ ድርሻ ለዓለም አቀፍ ባለሃብቶች ለማቅረብ ያለመ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ኩባንያዎችም የማይመለስ 20 ሺህ ዶላር እና መተማመኛ በ13 ቀናት ውስጥ ማቅረብ እንደሚችሉም ነው የገለጸው።

የጨረታ ሰነዳቸውን telecombid@mofed.gov.et በመግባት ማቅረብ እንደሚችሉ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version