Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከ66 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጅግጅጋ እና ድሬደዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች 66 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸው ተገለጸ፡፡

የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከታኅሣሥ 25 እስከ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ከ12 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የተለያዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎችን ይዟል፡፡

በተመሳሳይ በድሬደዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከ54 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በሕገወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጡ ሲሉ በተለያዩ ኬላዎች መያዛቸውን የጉሙሩክ ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

 

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version