ኮሮናቫይረስ

በሳምባ ኢንፌክሽን ዛሬ ማለዳ ህይወታቸው ያለፈው የ68 ዓመት ኢትዮጵያዊ የኮሮና ቫይረስ እንዳልነበረባቸው በምርመራ ተረጋገጠ

By Tibebu Kebede

April 01, 2020

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 23 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳምባ ኢንፌክሽን ዛሬ ማለዳ ህይወታቸው ያለፈው የ68 ዓመት ኢትዮጵያዊ የኮሮናቫይረስ እንዳልነበረባቸው በላብራቶሪ በምርመራ መረጋገጡን ነው የጤና ሚኒስቴር የገለጸው።

የጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ዶክተር ተገኔ ረጋሳ እንደተናገሩት ግለሰቡ የሳምባ ኢንፌክሽን እንዳለባቸው ቢታወቅም የኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ስለመሆን አለመሆናቸው ለማረጋገጥ ናሙናቸው ተወስዶ ምርመራ ተደርጎበታል።