የሀገር ውስጥ ዜና

በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች ተቋርጦ የነበረው የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም እንዲጀምር መደረጉን የክልሉ መንግስት ገለፀ

By Tibebu Kebede

March 31, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በምእራብ ኦሮሚያ በሚገኙ ዞኖች ውስጥ በተወሰኑ አካባቢዎች ላይ ተቋርጦ የነበረው የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም እንዲጀምር መደረጉን የክልሉ መንግስት ገለፀ።

የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ፥ በአካባቢዎቹ የቴሌኮም አገልግሎት ዳግም ወደ ስራ እንዲመለስ የክልሉ መንግስት እና የፌደራል መንግስት በጋራ ሲሰሩት የነበረው ስራ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።