Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዓለም አቀፉ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት ማጠቃለያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው

 

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 25 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት አከባበር በኢትዮጵያ ማጠቃለያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በመርሃ ግብሩ ሚኒስትሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

በመድረኩ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሡ ጥላሁን፥ ሳምንቱ ስኬታማ እንደነበር መግለፃቸውን ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ለስራ ፈጣሪዎች አስቸጋሪ የሆኑ አሰራሮች እና ዕድሎች ላይ ውይይት እንደሚደረግ፣ በሳምንቱ በተከናወኑ ውድድሮች ላይ አሸናፊ ለሆኑት ዕውቅና እንደሚሰጥና ከሕዳር እስከ ሕዳር የሚከናወኑ ተግባራት ይፋ እንደሚሆንም አቶ ንጉሱ አመላክተዋል፡፡

በመድረኩ የተገኙት የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ፥ በየዓመቱ ሕዳር ወር ላይ የሚስተናገደው ዓለም አቀፍ የኢንተርፕረነርሺፕ ሳምንት ለሚሊየን ችግሮች ሚሊየን ዕድሎች መኖራቸውን የሚያመላክቱ መርሃ ግብሮች የተከናወኑበት ሆኗል ብለዋል።

Exit mobile version