አዲስ አበበ፣ ሕዳር 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከተመድ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ እና ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ መኸመት ጋር ተወያዩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከስራ ሃላፊዎቹ ጋር በበርካታ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ምክክር ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል፡፡
በቀጣይም ከተቋማቱ ጋር በተጠናከረ መልኩ እንሰራለን የሚል እምነትእንዳላቸውም ነው የገለፁት፡፡