Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

1 ሺህ 21 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ ችግር ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 21 ኢትዮጵያውያን በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
 
ከተመላሾቹ ውስጥም 1 ሺህ 10 ወንዶች እና ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 9 ወንድ እና 2 ሴት ታዳጊዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡
 
ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉንም የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
 
በሁለት ቀናት በተከናወነው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ 2 ሺህ 193 ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉ ተጠቁሟል፡፡
 
Exit mobile version