አዲስ አበባ፣ መጋቢት 17፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ናይጄሪያ፣ ሱዳን እና ኢትዮጵያ ለህገወጥ ማታለል ስራ ተደራጅተው በማህበራዊ ድረገጽ በማታለል ወንጀል ላይ ተሰማርተው የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ግለሰቦቹ በዋናነት ሴቶችን በመተዋወቅና በማግባባት ከውጭ ሀገር የተለያዩ ስጦታ ልከናል ቀረጥና ማጓጓዣ በባንክ ከፍላቹ ውሰዱ በማለት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ አጭበርብረው በወስደው ተሰውረው የነበሩ ናቸው።