የሀገር ውስጥ ዜና

የአሸባሪው ህወሓት የሰሞኑ “ከአማራ ህዝብ ጋር ወዳጅ ነን” ፕሮፓጋንዳ አዲሱ የማምታቻ ስልት ነው – ምሁራን

By ዮሐንስ ደርበው

October 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከምስረታው ጀምሮ በአማራ ሕዝብ ላይ የተለያዩ ወንጀሎችን የፈጸመው አሸባሪው የህወሓት ቡድን አዲስ የማምታቻ ስልት ለመከተል እየሞከረ መሆኑን ምሁራን ገለጹ፡፡

ምሁራኑ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ የአማራ ሕዝብን በጠላትነት ፈርጆ ጥፋቶች መፈፀሙ ሳይረሳ ወዳጅ በማለት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ እያሰራጨ ነው፡፡