የሀገር ውስጥ ዜና

ለመጠጥ ውሃ፣ ሳኒቴሽንና ሃይጅን ፕሮግራም ውጤታማነት የተቋማት ቅንጅታዊ አሠራር ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

October 20, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተቋማት መካከል ያለው ቅንጅታዊ አሠራር የመጠጥ ውሃ፣ ሳኒቴሽንና ሃይጅን ፕሮግራም ውጤታማ እንዲሆን ማስቻሉ ተገለጸ፡፡

በጋና አክራ እየተካሄደ በሚገኘው “All System Go Africa” ሲምፖዚየም ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ በፓናል ውይይት ወቅት እንደገለጹት÷ በኢትዮጵያ ለመጠጥ ውሃ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን ፕሮግራም ውጤታማነት የመንግሥት ቁርጠኝነትና በተቋማት መካከል የተፈጠረው ቅንጅታዊ አሠራር ተጠቃሽ ነው፡፡