የሀገር ውስጥ ዜና

የእቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ወደ ሙሉ ትግበራ ሊገባ ነው

By ዮሐንስ ደርበው

October 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2014 በጀት ዓመት በሙከራ ደረጃ የተጀመረው የእቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ወደ ሙሉ ትግበራ ሊገባ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የሙከራ ትግበራውን አፈፃጸም በመገምገም ወደ ሙሉ ትግበራ ለመሸጋገር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ዛሬ ከአጋሮችና ባለድርሻዎች ጋር በአዲስ አበባ ምክክር እየተደረገ ነው፡፡