የሀገር ውስጥ ዜና

የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል “ሄቦ” እየተከበረ ነው

By ዮሐንስ ደርበው

October 02, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ በዓል “ሄቦ”በጥንታዊው አንገሪ ቤተ መንግስት በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል፡፡

የዓመቱ የመጀመሪያ ወር የሚል ትርጉም ያለው “ሄቦ” የብሔረሰቡ ተወላጆች እንዲሁም የፌደራልና ክልል የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ነው፡፡