የሀገር ውስጥ ዜና

ከሰሞኑ “የሰብዓዊ መብት ጥሰት” በሚል የወጣው ሪፖርት ፖለቲካዊ ሸፍጥ አለበት – የሕግ ምሁራን

By ዮሐንስ ደርበው

September 21, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሰሞኑ “የሰብዓዊ መብት ጥሰት” በሚል የወጣው ሪፖርት ከሣይንሳዊ መንገድ ይልቅ ፖለቲካዊ ሸፍጥን የተከተለ ነው ሲሉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በተሠራው ምርምር የተሳተፉ የሕግ ምሁራን ተናገሩ፡፡

ምሁራኑ ለፋና ብሮድካስንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ አሸባሪው ህወሓት በርካታ ጥፋቶችን ማድረሱን የሚያረጋግጡ መረጃዎች ቢኖሩም በሪፖርቱ እንዳልታዩ ታልፈዋል፡፡