አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል የፀጥታው ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የክልሉን ሰላምና ፀጥታን ለማጎልበት የተከናወኑ ተግባራት ገምግሟል።
በውይይቱም የክልሉን ሰላምና ፀጥታን ከማጠናከር አንፃር በተለይም ህገወጥ የጦር የመሳሪያ ዝውውር፣ የኮንትሮባንድ ንግድ፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውርና የነዳጅ ግብይትን ከመከላከል አንፃር የተከናወኑ ተግባራትን በሚመለከት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።