የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካ ወጣቶችን የማስተሳሰር መርሐግብር ይፋ ሆነ

By ዮሐንስ ደርበው

September 19, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋራ የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ የኢትዮጵያውያንና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ወጣቶችን የማስተሳሰር መርሐ ግብር ይፋ አድርጓል ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል አባል እና የብሔራዊ ኮሚቴው ጸሐፊ አክሊሉ ታደሰ እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ሀገራት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ፍስሐ ሻወል በጉዳዩ ላይ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡