Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የእውቅና ሽልማት መርሐ-ግብር አካሄደ

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 7 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የእውቅና ሽልማት መርሐግብር በሚሊኒየም አዳራሽ አካሄደ።

በመርሐ-ግብሩ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረ ሚካኤል፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የኢትዮ- ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህወት ታምሩን ጨምሮ የተለያዩ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

እውቅናና ሽልማቱ የተሰጠው በሀገሪ ወንጀል መካከል ተግባር በአመራርነትና፣ በአዛዥነትና በጀግንነት የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት መሆኑ ተመላክቷል።

እውቅናና ሽልማቱ የተበረከተው በጠቅላይ መምሪያው 24 ክፍሎችና እና በስሩ ለሚገኙ 6 ተጠሪ ክፍሎች መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version