የሀገር ውስጥ ዜና

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ “ለአፍሪካውያን ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ” መርሕ ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

By ዮሐንስ ደርበው

September 15, 2022

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “ለአፍሪካውያን ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ” መርሕ በአፍሪካ ሕብረት አማካኝነት ለሚደረገው የሰላም ድርድር ሂደት ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርግ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ጠየቁ፡፡

በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በቤጂንግ ለሚገኙ የአውሮፓ ሕብረት አባል ሀገራት፣ የአሜሪካ፣ የእንግሊዝ፣ የካናዳ እና ኖርዌይ ዲፕሎማቶች በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡