የሀገር ውስጥ ዜና

የጠላትን ሀገር የማፍረስ ፍላጎት በመመከታችን ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጪ የልማት ውጥኖችን እውን እያደረገች ነው – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

By ዮሐንስ ደርበው

September 09, 2022

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠላቶቻችንን ሀገር የማተራመስና የማፍረስ ፍላጎት በተቀናጀ ትግልና ተጋድሎ በመመከታችን ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጪ የሆኑ የልማት ውጥኖችን እውን እያደረገች ነው ሲሉ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ፡፡

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ “መከታ” በተሰኘው የመከላከያ ሠራዊት መጽሔት ላይ ለአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡