የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ በበጎ ፈቃድ አርዓያ ተግባር ለፈጸሙ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅናና ምስጋና ተሰጠ

By Feven Bishaw

September 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በተከበረው “የበጎ ፍቃድ ቀን” በአዲስ አበባ ከተማ በተለየዩ መስኮች በበጎ ፈቃደኝነት አርዓያ ተግባር የፈጸሙ ተቋማትና ግለሰቦች ከከተማ አስተዳደሩ እውቅናና ምስጋና ተሰጥቷቸዋል፡፡

በእውቅናና ምስጋና መርሐ ግብሩ በጎ ፍቃደኞችን ያመሰገኑት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ ለሕዝቦች ሰላም ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን እየሰጡ ላሉት የመከላከያ ሠራዊቱና ጥምር ኃይሉ ምስጋና አቅርበዋል።