የሀገር ውስጥ ዜና

ኢንዱስትሪ ፓርኩ የሀገር መከላከያ ሰራዊትና የኦሮሚያ ልዩ ሀይል ዩኒፎርሞችን ማምረት ጀመረ

By Feven Bishaw

August 31, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሀይል ወታደራዊ ዩኒፎርም (መለዮ) በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ መመረት መጀመራቸውን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡

የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳንዶካን ደበበ፣ የኮርፖሬሽኑ የትራንስፎርሜሽንና ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍፁም ከተማ እንዲሁም ሌሎች የስራ ሀላፊዎች የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን ጎብኝተዋል፡፡