የሀገር ውስጥ ዜና

ከ76 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

By Feven Bishaw

August 21, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከነሐሴ 6 እስከ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከ76 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የገቢና የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ከዚህ ውስጥ 66 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር የሚገመተው የገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች ሲሆኑ፥ 10 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የሚያወጡት ደግሞ የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡