የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ክልል እና ዩ ኤን ዲ ፒ በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ

By ዮሐንስ ደርበው

August 17, 2022

 

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩ ኤን ዲ ፒ) በጋራ ለመሥራት ተፈራርመዋል፡፡

ስምምነቱን፥ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ ቶሎሳ ገደፋ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ቱርሃን ሳለህ ናቸው የተፈራረሙት፡፡