የሀገር ውስጥ ዜና

የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ጸደቀ

By Feven Bishaw

August 15, 2022

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የከፍተኛ ትምህርት አገራዊ ቅድመ ምረቃ የመውጫ ፈተናን በአግባቡ ለመምራትና ለማስተዳደር የተዘጋጀው የፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ጸደቀ።

የትምህርት ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ መመሪያው በመውጫ ፈተና ዝግጅት ሊካተቱ ስለሚገባቸው ሀገራዊ ዝቅተኛ የትምህርት ብቃት መመዘኛዎችን ፣ የሙያ ሥነምግባር ደምቦችን እና ተቋማት ሊከተሏቸው የሚገቡ የአሠራር ስነ- ስርዓቶችን አካቷል ።